Thursday, January 10, 2019

ወለጋ ላይ ጦርነት አዲስ አበባ ላይ ሰላማዊ ትግል የሚለው አካሄድ ተቀባይነት የለውም ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 2/2011)ወለጋ ላይ ጦርነት አዲስ አበባ ላይ ሰላማዊ ትግል የሚለው አካሄድ ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም ሲል የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ኦዴፓ አስታወቀ።

የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ዓለሙ ስሜ ለኢሳት እንደገለጹት በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው ኦነግ በወለጋ ውጊያ እያደረገ በአዲስ አበባ ስለ ሰላማዊ ትግል መናገር አይቻልም ብለዋል።
ሸኔ ኦነግ ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ በሶስተኛ ወገን እንደራደር ማለቱን በተመለከተ የፓርቲያቸውን አቋም የገለጹት ዶክተር ዓለሙ ስሜ ከእንግዲህ ድርድር የሚባል ነገር የለም መሳሪያውን አስቀምጦ በምርጫ ቦርድ በሚደረግ የፓርቲዎች ንግግር ላይ መሳተፍ ይችላል ሲሉ ጥሪውን ውድቅ አድርገዋል።

በኦሮሚያ ክልል በወለጋና በጉጂ ሰላም መስፈኑን፣ ሁሉ ነገር ወደ ቀድሞው ሰላማዊ ህይወት መመለሱን የገለጹት ዶክተር አለሙ ዛሬ በአቶ ገላሳ ዲልቦ ከሚመራው ኦነግ ጋር የተደረገውም ውይይት ውጤታማ እንደሆነ ገልጸዋል።

በብርጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘውና በግብረ አበሮቻቸው ላይ ክስ ተመሰረተ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 2/2011) በብርጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘውና በግብረአበርነት በተያዙት የሜቴክ የስራ ሃላፊዎች ላይ ዛሬ በይፋ ክስ መመስረቱ ተሰማ።

በተለያዩ ሰባት የሙስና ወንጀሎች በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 5ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሰረተባቸው ብርጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው፣ብርጋዴር ጄኔራል ጠና ቁንዲ፣ረመዳን ሙሳ፣ኮለኔል ደሴ ዘለቀ፣ቸርነት ዳናን ጨምሮ 8 ሰዎች መሆናቸው ተመልክቷል።

Wednesday, January 9, 2019

በመከላከያ ሰራዊት የሚመራ ኮማንድ ፖስት ሊቋቋም ነው

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 30/2011) በኢትዮጵያ በአንዳንድ የሃገሪቱ ክልሎች ያለውን የጸጥታ ችግር ለመፍታት በመከላከያ ሰራዊት የሚመራ ኮማንድ ፖስት በመቋቋም ላይ መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትሯ ገለጹ።

የሃገር መከላከያ ሚኒስትሯ ኢንጂነር አይሻ መሃመድ ለፓርላማው ዛሬ እንደገለጹት በክልሎች ጥያቄ ጸጥታ ወደ ደፈረሰባቸው አካባቢዎች የገባው የመከላከያ ሰራዊት የህዝቡን ደህንነት ለማስጠበቅ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።
ባለፉት 6 ወራት ከ7ሺህ በላይ የሰራዊት አባላት መሰናበታቸውንም ገልጸዋል።
ቦታዎቹ ወይንም ክልሎቹ የትኞቹ እንደሆኑ የመከላከያ ሚኒስትሯ ባይገልጹም በኦሮሚያና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ድንበር እንዲሁም በጉጂ ዞን የመከላከያ ሰራዊት መሰማራቱ ታውቋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር/ኦነግ/ ጋር የጀመረው ውዝግብ መፍትሄ ሳያገኝ በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት የመከላከያ ሰራዊት የጸጥታ ችግር ወዳለባቸው አካባቢዎች እንዲሰማራ መደረጉ መንግስት የኦነግን እንቅስቃሴ በሃይል ለማስቆም መወሰኑን ያሳያል ተብሏል።
የሃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች ችግሩን በሰላም ለመቋጨት በርካታ ጥረቶች ማድረጋቸውም ይታወሳል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከመምህራን ጋር ባለፈው ሳምንት ባደረጉት ውይይት የኦነግን እንቅስቃሴ ለወራት በትዕግስት ሲያዩት መቆየታቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
20 እና 30 ዓመታት ምንም ፍሬ በማያፈራ ሁኔታ ውስጥ ካለበት በክብር ያመጣናቸው በኤርትራና በሶማሊያ ያደረጉት የነበረውን ጦርነት ወለጋ ውስጥ እንዲያመጡት አይደለም ማለታቸው አይዘነጋም።
በሌላም በኩል የሃገር መከላከያ ሚኒስትሯ ዛሬ በፓርላማ ባቀረቡት ሪፖርት ባለፉት 6 ወራት 7 ሺህ 17 የሰራዊቱ አባላት መሰናበታቸውን ገልጸዋል።
ተሰናባቾቹም በዕድሜ የማዕረግ ዕድገት ፈተናን ባለማለፍ እንዲሁም በትምህርት ደረጃቸው ዝቅተኛነት የተሰናበቱ መሆናቸውን አመልክተዋል።

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን በገንዳ ውሃ ከተማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በትላንትናው ዕለት በከፈቱት ተኩስ ዘጠኝ ሰዎች መሞታቸው እና 15 መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ለDW ገለጹ።

 ድርጊቱን በመቃወም ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡት የከተማይቱ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው የሰፈረው የመከላከያ ሰራዊት ከስፍራው ለቅቆ እንዲወጣ ጠይቀዋል። DW Amharic

የመንግስት ሰራተኛ የሆኑ አንድ የዓይን እማኝ እንደተናገሩት የመከላከያ ሰራዊት አባላት በነዋሪው ላይ ተኩስ የከፈቱት በነዋሪዎች ታግተው የነበሩ የሱር ኮንስትራክሽን ድርጅት ተሽከርካሪዎችን ለማስለቀቅ በሚል ነበር። “የመከላከያ ሰራዊት የእሩምታ ተኩስ ተኩሶ ጉዳት አድርሷል። ባለኝ መረጃ መሰረት ህጻናትን ጨምሮ ወደ 15 ገደማ የሚሆኑ የቆሰሉ ሲሆን የሟቾቹ ቁጥር ዘጠኝ ደርሷል” ሲሉ እኚሁ የከተማይቱ ነዋሪ ተናግረዋል።

የሞቱትም ሆነ የተጎዱ ሰዎች ወደ ገንዳ ውሃ መተማ ሪፈራል ሆስፒታል መወሰዳቸውን የሚናገሩት የዓይን እማኙ ከማቾቹ ውስጥ የስድስት ሰዎችን አስክሬን መመልከታቸውን ገልጸዋል። “እኔ ስድስት ሰዎች ተመልክቻለሁ። እስከ ምሽት ሁለት ሰዓት እስከነበርኩበት ድረስ ከገንደ ውሃ ከተማ አንዲት ህጻንን ጨምሮ ሶስት ሰዎች፣ ከኮኪት ከተማ ደግሞ ሶስት ሰዎች ነበሩ” ሲሉ እማኝነታቸውን ሰጥተዋል። ከቆሰሉት ውስጥ በእርሻ ስራ ላይ ቆይተው ሲመለሱ የነበሩ የቀን ሰራተኞች አሉበት ብለዋል።

የገንደ ውሃ ከተማ ነዋሪዎች የመከላከያ ሰራዊትን እርምጃ በመቃወም ዛሬ አደባባይ ወጥተዋል። ከጠዋት እስከ እኩለ ቀን ድረስ በዘለቀው ተቃውሞ ይሰሙ ከነበሩት መፈክሮች ውስጥ “የወህሓት መከላከያ እኛን አይወክልም፤ በፍጥነት ይውጣልን”፣ “በአማራነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ይቁም” የሚሉ እንደሚገኙበት ከሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች አንዱ ተናግረዋል።

ሰልፈኞቹ ትላንት ወደ ኮኪት ከተማ እንዲወሰዱ የተደረጉት የሱር ኮንስትራክሽን ተሽከርካሪዎች ወደ ገንደ ውሃ ከተማ እንዲመለሱ እንዲደረግ እና አስፈላጊውን ማጣራት እንዲደረግባቸው መጠየቃቸውን የከተማይቱ ነዋሪ ገልጸዋል። በተቃውሞ ምክንያት ከአዘዞ እስከ መተማ የሚዘልቀውን አውራ ጎዳና መዘጋቱንም ጨምረው አስረድተዋል። ለተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ምላሽ ለመስጠት የአካባቢው አስተዳደርም ሆነ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮች በስፍራው አለመገኘታቸውንም አክለዋል።

Wednesday, January 2, 2019

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጠ

ተቋሙ በኦሮሚያ ክልል በቡራዩ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ እና በደቡብ ክልል  የተፈጸመውን ወንጀል አስመልክቶ ተከሰቶ የነበረው ሁከትና ብጥብጥ መነሻ ጉዳያቸውን ሲያጣራ ቆይቶ የምርመራ ሥራ መጠናቀቅን አስመልክቶ፣ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ለህግ ታራሚዎች የተሰጠ ይቅርታ እንዲሁም የምህረት አዋጅ ሀገር አቀፍ አፈጻጸም ወቅታዊ መረጃ አሰመልክቶ ታህሳስ 24 ቀን 2011 ዓ.ም በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ መሰብሰቢያ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጠ፡፡

Tuesday, December 18, 2018

አምዶም ገብረስላሴ ታሰረ

ባለፈው ቅዳሜ በመቀሌ በተካሄደው ስብሳባ አቶ በረከት ስሞኦን እና የሕወሓት ባለስልጣናትን የተቸው አምዶም ገብረስላሴ ታሰረ።
     ለኢሳት በደረሰው መረጃ መሰረትየአረና የሕዝብ ግኑኝነት ሃላፊ አቶ  አምዶም ገብረስላሴ በቁጥጥር ስር የዋለው መቀሌ አክሱም ሆቴል በተባለው አካባቢ ሲሆን፣ሰው ደብድበሃል በሚል  መታሰሩንም  መረዳት ተችሏል።አምዶም  መቀሌ አዲሸንዲህ በተባለ  ቦታ እንደታሰረ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።አምዶም ገብረስላሴ ባለፈው ቅዳሜ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ በተካሄደው  ሰብሰባ የሕወሃትን ባለስልጣናት ሲተች ንግግሩ እንዲቋርጥ መደረጉም ይታወሳል።

Friday, December 14, 2018

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ በተከሰተ ግጭት እስካሁን የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ፡፡

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ በተከሰተ ግጭት እስካሁን የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ፡፡ ከአንድ መቶ የሚበልጡ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል ተብሏል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሡ ዳምጠው ዛሬ ለሸገር እንደተናገሩት ከትናንት በስትያ አንስቶ በቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ ግጭት ተከስቷል፡፡ በግጭቱ እስከ አሁን የ13 ሰዎች ህይወት ማለፉ የተነገረ ሲሆን ከአንድ መቶ የሚበልጡ ደግሞ ቆሰለዋል ተብሏል፡፡ በንብረት ላይም ጉዳት መድረሱን አቶ አድማሱ ተናግረዋል፡፡

Thursday, December 13, 2018

ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ክፍል መዘጋቱ ተረጋገጠ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 4/2011) ማዕከላዊ በመባል የሚጠራው የወንጀል ምርመራ ክፍል መዘጋቱን አረጋግጬአለሁ ሲል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።

ኮሚቴው ማዕከላዊን ተዘዋውሮ ከጎበኘበኋላ በሰጠው መግለጫ ማዕከላዊ ተዘግቶ ክፍሎቹ ለቡራዩ ተፈናቃዮች በጊዜያዊ መኖሪያነት እያገለገሉ ነው ብሏል።
የኮሚቴው አባላት አረጋገጥን እንዳሉትም በማዕከላዊ አንድም እስረኛ የለም።

በአዲስ አበባ ከ2ሺህ በላይ ነዋሪዎች ቤተክርስቲያን መጠለላቸው ታወቀ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 4/2011) ከአዲስ አበባ በተለምዶ አጃምባ በሚባል አካባቢ ቤት ሰርተው ለዓመታት የቆዩ ከ2ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተፈናቅለው ቤተክርስቲያን መጠለላቸውን ገለጹ።

ህገወጥ ናችሁ ተብለው በሌሊትበተኙበት በአፍራሽ ግብረሃይል ቤታቸው የፈረሰባቸው ተፈናቃዮች በፋኑዔል ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተጠልለው መኖር ከጀመሩ 15ቀናትያለፋቸው መሆኑን ለኢሳት ገልጸዋል።
በወቅቱ በድንገት በተወሰደው የማፍረስ ተግባር በተፈጠረ ግርግር

Monday, December 3, 2018

ፖሊስ ሜጀር ጀኔራል ክንፈ ዳኘው የተጠረጠሩባቸውን ተጨማሪ የወንጀል ተሳትፎዎች አቀረበ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 24 ፣ 2011 (ኤፍ ቢ ሲ) መርማሪ ፖሊስ ሜጀር ጀኔራል ክንፈ ዳኘውን በተመለከተ እስካሁን በሰራው የምርመራ ስራ አገኘኋቸው ያላቸውን ተጨማሪ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤት አቅርቧል።

ፖሊስ በዛሬው እለት ግለሰቡን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ካቀረባቸው ማስረጃዎች በተጨማሪነት አዳዲስ ያላቻውን ነው ያቀረበው።

በአፋር ክልል በተቀሰቀሰ ግጭት አንድ የአፋር ወጣት ተገደለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በአፋር ክልል በመሬት ይገባኛል ጥያቄ ኤል ውሃ አካባቢ ቡርካ በሚባል ቦታ በተቀሰቀሰ ግጭት ሰላም ለማስከበር በሚል ጣልቃ በገባ የመከላከያ ሰራዊት አንድ የአፋር ወጣት መገደሉን ለኢሳት የደረሰ መረጃ አመልክቷል።

በአፋር ዛሬ የሚጀመረውንና አብዛኛውን አመራሮችን ያሰናብታል ተብሎ የሚጠበቀው የክልሉ ገዢ ፓርቲ ጉባዔውን በሚያካሂድበት ወቅት ዋዜማ የተቀሰቀሰው ግጭት ሶስተኛ ቀኑን መያዙ ታውቋል።
ጉባዔውን በሁከት በማጀብ የአቶ ስዩም አወል ቡድን የሚፈጽመው ሴራ ሳይሆን አይቀርም ተብሏል።

በቤንሻንጉልና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ጥቃት የሚፈጽመው ኦነግ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በቤንሻንጉል ጉምዝና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ጥቃት በመፈጸም ላይ ያለው የኦነግ ጦር መሆኑን የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አስታወቀ።
ለእርዳታ የተዘጋጀ ከ2ሚሊዮን ብር በላይ በታጣቂዎች መዘረፉም ታውቋል።
በሁለቱ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ውጥረት ቀጥሏል።
መከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ በግጭቱ አካባቢዎች መስፈራቸውን የቤንሻንጉል ጉምዝ ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ሰይፈዲን ሀሩን  ለኢሳት ገልጸዋል።

የወልቂጤ አካባቢ ወጣቶች በልዩ ሃይል እየታፈሱ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በጉራጌ ዞን የወልቂጤ አካባቢ ወጣቶች በአካባቢው ልዩ ሃይል እየታፈሱ መሆኑ ተሰማ።
በጉራጌና በቀቤና ብሔረሰቦች መካከል ቀደም ሲል ተቀስቅሶ የነበረው ግጭትም አሳሳቢ ወደሚባል ደረጃ እየተሸጋገረ መሆኑን ኢሳት ወደ አካባቢው ደውሎ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በፌደራል ደረጃ ጉዳዩን ለመፍታት የተደረገው ሙከራ ሊሳካ አልቻለም የሚሉት የኢሳት ምንጮች ግጭቱ እንዲባባስ የሚፈልጉ አካላት ደግሞ በአካባቢው ውጥረት እየፈጠሩ ነው ብለዋል።
ሁኔታውን ለማረጋጋት የፌደራሉ መከላከያ ሃይል በአካባቢው መሰማራቱም ታውቋል።

የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦች ግንኙነት የበለጠ መጠናከር አለበት ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011)የኢትዮጵያ ችግር ከስረ መሰረቱ እንዲነቀል የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦች ግንኙነት የበለጠ መጠናከር እንዳለበት የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ገዱ አንዳርጋቸው ገለጹ።
በአቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተመራው የአማራ ክልል የልኡካን ቡድን በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ካለው የአማራ ተወላጆችና የአማራ ጉዳይ ያገባናል ካሉ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ምክክር አድርገዋል።
ከስብሰባው ተዳሚዎች ለቀረቡ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ችግር ከስረ መሰረቱ እንዲነቀል የእነዚህ ህዝቦች ግንኙነት የበለጠ የኦሮሞና የአማራ ህዝቦች በትንሹ መገናኘት ሲጀምሩ፥መቻቻል ሲጀምሩ በሀገሪቱ ላይ ምን ያህል ተጽዕኖ ማምጣት እንደሚችሉ አሳይተውናል።

አርበኞች ግንቦት ሰባት በመጪው ምርጫ በ547 ወረዳዎች ለመወዳደር ማቀዱን አስታወቀ

አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ በመጪው ምርጫ በ547 ወረዳዎች ዕጩዎቹን ለማቅረብ መዘጋጀቱን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ተናገሩ።ንቅናቄው በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በንቃት የሚያሳትፍ ድርጅት ሊመሰርት መዘጋጀቱንም አቶ አንዳርጋቸው ጨምረው ተናግረዋል።
አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ በመጪው ምርጫ በ547 ወረዳዎች ዕጩዎቹን ለማቅረብ መዘጋጀቱን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ተናገሩ። አቶ አንዳርጋቸው ይኸን ያሉት ንቅናቄው በብሪታኒያ እና አካባቢዋ ከሚገኙ አባላቱ ጋር በመከረበት ስብሰባ ላይ ነው። ንቅናቄው በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በንቃት የሚያሳትፍ ድርጅት ሊመሰርት መዘጋጀቱንም አቶ አንዳርጋቸው ጨምረው ተናግረዋል። አዲስ የሚቋቋመው ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ እና መርሐ-ግብር በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ውስጥ ዝግጁ ይሆናሉም ተብሏል። በትናንትናው ዕለት በለንደን ከተማ የተካሔደውን ውይይት የተከታተለችው ሃና ደምሴ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች። 

Friday, November 30, 2018

የሰራዊቱ አባላት ወታደራዊ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ከወር በፊት ያለ ፈቃድ ወደ ቤተመንግስት የተንቀሳቀሱ ወታደሮችን ያስተባበሩ የሰራዊቱ አባላት ወታደራዊ ፍርድ ቤት ቀረቡ። ከወታደራዊ ዲሲፒሊን በማፈንገጥና ሕግን በመጣስ የተንቀሳቀሱትን ወገኖች በሕግ ተጠያቂ ማድረግ ነገ ተመሳሳይ ነገር እንዳይፈጸም ይከላከላል ሲሉ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ ገልጸዋል።

Wednesday, November 28, 2018

U.S. Assistant Secretary of State visits Ethiopia

 ESAT News (November 28, 2018)
US Assistant Secretary of State for African Affairs, Tibor Nagy is in Addis Ababa for an official working visit as part of his tour to East Africa.
Nagy and General Thomas D. Waldhauser, Commander of U.S. Africa Command (AFRICOM), met with Ethiopia’s Minister of Defense Aisha Mohammed to discuss opportunities for security cooperation between the United States and Ethiopia, according to the U.S. Embassy in Addis Ababa.
Speaking to NPR’s “All Things Considered” a week ago, Mr. Nagy called Ethiopia’s Prime Minister Abiy Ahmed “visionary.”
“It shows you what one courageous, visionary leader can do to impact not only her or his own country, but the region,” Nagy said speaking about Ahmed who is credited for reforms in his country and ending a two decae old animosity with Eritrea.
“Now the waves are kind of washing over other parts of the region. I mean, during my discussions with African leaders, I pointed to Ethiopia as – what a positive force can mean for Africa.”
It is Nagy’s first visit to Ethiopia since his confirmation in July. He served as U.S. Ambassador to Ethiopia from 1999 to 2002

Wednesday, November 21, 2018

ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ከህዝቡ ጎን በመሰለፍ አርአያነታችንን እናስመስክር አሉ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 11/2011) በኢትዮጵያ አሁን የተገኘው ለውጥ በሁሉም ህዝብ ትግል የመጣ በመሆኑ እኛም ከህዝቡ ጎን በመሰለፍ አርአያነታችንን ማስመስከር ይገባናል ሲሉ ጀነራል ሰዓረ መኮንን ገለጹ።
የኢትዮጵያ የሃገር መከላከያ ሚኒስቴር ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ጄነራል ሰዓረ መኮንን በአንድ የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ የመጣው ለውጥ የሁሉንም ሕዝብ ተሳትፎ የጠየቀ በመሆኑ ሰራዊቱም የዚህ ለውጥ ተጠቃሚ እና ደጋፊ ነው ።
በለውጡ የሰራዊቱን ኑሮ ከማሻሻል ጀምሮ ለአከባቢው ሰላም የነበረን ሚና ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ መቀመጡንም ገልጸዋል።
እናም ከለውጡ ጋር መሄድና የዘመናዊ ሰራዊት ግንባታን ማፋጠን ይገባናል ብለዋል።
ጠቅላይ ኢታማጆር ሹም ሰዓረ መኮንን እናደሉት የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግል ላገኘው ለውጥ መከላከያ ሰራዊቱ አጋርነቱን ያረጋገጣል።
እኛ ለሕዝባችን የመጨረሻ ምሽግ ነን ሲሉም ሰራዊቱ ከለውጡ እና ከሕዝቡ ጋር መቆሙንም አረጋግጠዋል።

በሜቴክ ሳቢያ የ36 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ አስከተለ

(ኢሳት ዲሲ–ህዳር 12/2011)የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን በአፋር ክልል እገነባዋለሁ በማለት የተንቀሳቀሰበት የእንፋሎት ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በሜቴክ ሳቢያ የ36 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ ማስከተሉ ተገለጸ።

በጄኔራል ክንፈ ዳኘው ይመራ የነበረው ሜቴክ ከኮንትራት ስምምነቱ ውጪ ከውጭ ያስገባቸው መሳሪያዎች አሮጌዎችና ያልተሟሉ በመሆናቸው ለፕሮጀክቱ መክሸፍና ለተከተለው ኪሳራ ምክንያት እንደሆነም መረዳት ተችሏል።
137 ሜጋ ዋት ያመነጫል የተባለው የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም መክሸፉ ተመልክቷል።

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ሆነው ሊሾሙ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 12/2011) ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በነገው ዕለት የሀገሪቱ የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ሆነው እንደሚሾሙ ተገለጸ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ በሚያደርገው ስብሰባ ወይዘሪት ብርቱካንን የምርጫ ቦርዱ ሀላፊ እንዲሆኑ በጠቅላይ ሚንስትር አብይ የሚቀርበውን ሀሳብ መነሻ በማድረግ ድምፅ ይሰጣል ተብሏል።
ወይዘሪት ብርቱካን ከሰባት አመታት ስደት በኋላ መንግስት ባደረገላቸው ጥሪ በቅርቡ ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸው ይታወሳል።
ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እንደ አዲስ ለሚደራጀው ብሔራዊ ምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ኃላፊ እንዲሆኑ መታጨታቸው ሲነገር ቆይቷል ።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ  ስያሜውንና አጠቃላይ አደረጃጀቱን በማሻሻል ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ ሆኖ ይቋቋማል ተብሎ ይጠበቃል።