Thursday, November 17, 2016

CPJ renews calls to Ethiopian regime to release all journalists

Ethiopia should immediately release all journalists detained amid an intensifying crackdown on the media, the Committee to Protect Journalists said on Thursday.
In recent weeks, Ethiopian authorities have jailed Getachew Worku, newspaper editor, as well as two members of the award-winning Zone 9 bloggers’ collective, which has faced continuous legal harassment on terrorism and incitement charges.
A fourth journalist has been missing for a week; his family fears he is in state custody, CPJ said in a state
“Silencing those who criticize the government’s handling of protests will not bring stability,” CPJ Africa Program Coordinator Angela Quintal said from New York. “The constant pressure on Zone 9 bloggers with repeated arrests and court appearances is clearly designed to intimidate the remaining independent journalists in Ethiopia.”

የአርበኞች ግንቦት7 ሃይል ከህወሃት/ኢህአዴግ ወታደሮች ጋር በቀብትያ ሁመራ እና አጎራባች ቀበሌዎች እየተዋጋ ነው

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአርበኞች ግንቦት7 የሰሜን ጎንደር አስተባባሪ እንደገለጹት፣ አባሎቻቸው በሰሜን ጎንደር በተለያዩ አካባቢዎች ለወራት ሲደራጁና ሲያደራጁ ከቆዩ በሁዋላ፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ወታደራዊ ጥቃት በመፈጸም ላይ ናቸው። በተለይ ከትናንት ጀምሮ በቃፍታ ሁመራ እና በአከር አካባቢ ከፍተኛ ውጊያ እያካሄደ መሆኑንም ተናግረዋል።

በአባይ ግድብ አካባቢ ያለው የስራ እንቅስቃሴ መዳከሙን ጋዜጠኞች ገለጹ ።

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ‹‹ በአባይ ግድብ ላይ ያለው እንቅስቃሴ ቆሟል የሚል ወሬ በስፋት እየተወራ ነውና ወሬውን አክሽፉ!” ተብለው ለጉብኝት የተላኩት ጋዜጠኞች ምንም አይነት የስራ እንቅስቃሴ ባለማየታቸው የሚወራው ትክክል መሆኑን አረጋጋጥው መመለሳቸውን ለኢሳት ገለጹ።
ሰሞኑን ወደ አባይ ግድብ የተላከው የ መንግስት ጋዜጠኞች ቡድን ለጉብኝት በቆየበት አንድ ቀን፤ ምንም አይነት ስራ ሲሰራ አለመመልከቱን ገልጿል፡፡ ‹‹ ለአንድም ደቂቃ ስራው አይስተጓጎልም ›› የተባለለት ይህ የግድብ ስራ አልፎ አልፎ ከሚንቀሳቀሱ ተሸከርካሪዎች በስተቀር ምንም አይነት የስራ እንቅስቃሴም ሆነ ሰራተኞችን አለመመልከቱንና ስራው ተስተጓጉሏል የሚለው እውነት መሆኑን የቡድኑ አባላት ተናግረዋል።

በሶማሊያ ክልል በኮሌራ ወረሽኝ 35 ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በምስራቅ ኢትዮጵያ ኦጋዴን አካባቢዎች በኮሌራ በሽታ 35 ሰዎች መሞታቸውንና ድርቁን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊ ቀውስ እየተፈጠረ መሆኑን የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት አስታወቀ። በድርቁ ምክንያት እንስሳት እየሞቱ ነው። የምግብ እጥረት ተጠቂ የሆኑት የኦጋዴን ነዋሪዎች አፋጣኝ እርዳታ ካላገኙ አደጋው የከፋ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።

በኢንተርኔት አፈና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነች ።

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በዜጎቻቸው ላይ አፈና በማድረግ የመረጃ እቀባ ከሚያደርጉ አገራት ውስጥ ቻይና፣ ሶሪያ እና ኢራንን በመከተል ኢትዮጵያ በዓለም አራተኛ፣ በአፍሪካ ደግሞ በአንደኝኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ፍሪደም ሃውስ አስታውቋል። በኢንተርኔት ስርጭት ሁዋላ ቀር የሆነችው ኢትዮጵያ በኢንተርኔት ተጠቃሚ ዜጎቿ ላይ በምታደርገው እቀባዎችና አፈናዎች ግን ቀዳሚ ሆናለች ብሎአል።

ዮናታን ተስፋዬ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት እንደሚታሰር ታውቋል

ፌስቡክ ላይ በጻፋቸው ፅሁፎች ምክንያት የሽብር ክስ ቀርቦበት ጉዳዩ በፍ/ቤት እየታየ የሚገኘውና በእስር ቂሊንጦ ያለው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ በሚገኝበት እስር ቤት ውስጥ ከአርብ ህዳር 2/2009 ዓ.ም ጀምሮ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት ታስሮ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለዚህ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የዳረገው ህዳር 2/2009 ዓ.ም የፍርድ ቤት ቀጠሮ የነበራቸው እነ አቶ በቀለ ገርባ ወደ ፍርድ ቤት አንሄድም በሚል ከቂሊንጦ እስር ቤት አስተዳደር ጋር አለመግባባት ፈጥረው ድብደባ ሲደርስባቸው አቶ ዮናታን ‹‹ለምን ትደበድቧቸዋላችሁ፤ በመግባባት ቢሆን አይሻልም ወይ›› በሚል ለግልግል ጣልቃ መግባቱን ተከትሎ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋዬ በተለይ አብሮት የታሰረው አቶ አዲሱ ቡላላ ላይ ድብደባ ሲደርስበት ‹‹ተው አትደባደቡ›› በማለቱ ‹‹ምን አገባህ›› ተብሎ በራሱም ላይ ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞበት ከዚያ ወዲህ በሰንሰለት ለመታሰር እንደተዳረገ ታውቋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋየ ሰንሰለቱ የሚፈታለት ቤተሰቦቹ ሊጎበኙት ሲጠራ ብቻ እንደሆነም የመረጃው ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ አቶ ዮናታን መከላከያ ማስረጃዎችን ለማድመጥ ለህዳር 19/2009 ዓ.ም ተለዋጭ የፍ/ቤት ቀጠሮ ላይ እንደሚገኝ ይታወሳል፡፡

Wednesday, November 16, 2016

በቆላ ቃብቲያ ኹመራ ከፍተኛ ጦርነት ተቀስቅሷል

zehabesha
 ዛሬ ኅዳር 7 ቀን 2009 ዓ.ም ከቀኑ 11.00 አካባቢ ጀምሮ የወያኔ ጦር ከአማራ ገበሬዎች ላይ ጦርነት ከፍቷል። በአካባቢው የጎበዝ አለቆች የሚመራው የአማራ ገበሬዎች ጦር በአጋዚ ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ለማጥቃት የሄደው የወያኔ አጋዚ ጦር ከምልሻዎች እርዳታ መጠየቁን ሰምተናል።