ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት ዶ/ር መረራ ጉዲናን ለእስር መዳረጉን በሃገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ አለመረጋጋት ሊወስደው እንደሚችል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሃሙስ ገለጸ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) አመራር በቁጥጥር ስር መዋላቸው ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ የተካሄደ አፈና ነው ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ሃላፊ የሆኑት ሚቼሌ ካጋሪ አስታውቀዋል።
መንግስት የወሰደው ዕርምጃም በሃገሪቱ ያለውን ውጥረት እንደሚያባብሰው ያሳሰቡት ተወካዮዋ እርምጃው በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ ለሚከታተሉ አለም አቀፍ አካላት ጥሪን ያስተጋባ ነው ሲሉ አክለው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ዶ/ር መረራ ጉዲናን ለእስር መዳረጉን በሃገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ አለመረጋጋት ሊወስደው እንደሚችል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሃሙስ ገለጸ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) አመራር በቁጥጥር ስር መዋላቸው ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ የተካሄደ አፈና ነው ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ሃላፊ የሆኑት ሚቼሌ ካጋሪ አስታውቀዋል።
መንግስት የወሰደው ዕርምጃም በሃገሪቱ ያለውን ውጥረት እንደሚያባብሰው ያሳሰቡት ተወካዮዋ እርምጃው በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ ለሚከታተሉ አለም አቀፍ አካላት ጥሪን ያስተጋባ ነው ሲሉ አክለው ገልጸዋል።
