Thursday, December 1, 2016

የዶ/ር መረራ ጉዲና መታሰር በሃገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ አለመረጋጋት ሊወስደው እንደሚችል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት ዶ/ር መረራ ጉዲናን ለእስር መዳረጉን በሃገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ አለመረጋጋት ሊወስደው እንደሚችል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሃሙስ ገለጸ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) አመራር በቁጥጥር ስር መዋላቸው ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ የተካሄደ አፈና ነው ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ሃላፊ የሆኑት ሚቼሌ ካጋሪ አስታውቀዋል።
መንግስት የወሰደው ዕርምጃም በሃገሪቱ ያለውን ውጥረት እንደሚያባብሰው ያሳሰቡት ተወካዮዋ እርምጃው በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ ለሚከታተሉ አለም አቀፍ አካላት ጥሪን ያስተጋባ ነው ሲሉ አክለው ገልጸዋል።

ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲመቻች ጥሪ ቀረበ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባላት ህብረቱ ለእስር በተዳረጉት ዶ/ር መረራ ጉዲና ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲያመቻቹ ጥሪ ማቅረባቸውን ዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ ሃሙስ ዘገበ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር መረራ በኢትዮጵያ ተደንግጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መመሪያን ተላልፈው ተገኝተዋል በሚል ረቡዕ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
የፓርቲው አመራር ዶ/ር መረራ ከአንድ ሳምንት በፊት የአውሮፓ ህብረት ዋና መቀመጫ በሚገኝበት ብራሰልስ ተገኝተው ከህብረቱ የፓርላማ አባላት ጋር ውይይት ማካሄዳቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በሽያጭ በማቅረብ ላይ ነው ተባለ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት ለጎረቤት ደቡብ ሱዳን የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በሽያጭ በማቅረብ ላይ መሆኑን የሃገሪቱ አንድ የመገናኛ ብዙሃን ተቋም በብቸኝነት አግንቼዋለሁ ያለውን ሚስጢራዊ መረጃ ዋቢ በማድረግ አጋለጠ።

ባለፉት 10 ወራት ብቻ ወደ 90ሺ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በስደት የመን መግባታቸውን ተመድ ገለጸ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
ባለፉት 10 ወራቶች ብቻ ወደ 90ሺ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በስደት የመን መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን አስታወቀ።
ጦርነት ዕልባት ወዳላገኘባት የመን የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ስጋት እንዳደረሰባት የገለጸው ድርጅቱ ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ከ70ሺ የሚበልጡ ኢትዮጵያውያን ወደ ሃገሪቱ ገብተው እንደነበር አውስቷል።

Friday, November 25, 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በወያኔ ጦር ላይ በተለያዩ ቦታዎች በተደጋጋሚ ጥቃት መፈፀሙን በመቀጠል ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ታወቀ፡፡

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)

የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ነበልባል የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ህዳር 10 ቀን 2009 ዓ.ም ለሊት ጎንደር ዳንሻ ከተማ ልዩ ስሙ አዲስ አለም በተባለ ቦታ ሰፍሮ ከሚገኝ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ላይ በፈፀመው ድንገተኛ ማጥቃት ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ አጥቅቶ ተሰውሯል፡፡ በወሰደው ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃም 15 የወያኔ ቅጥረኛ ወታደሮችን በመግደል ቁጥራቸው ያልታወቀ ደግሞ ማቁሰሉን አርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን ከስፍራው ባደረሰን ዘገባ አስታውቋል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ጥቃቱን በመቀጠል ህዳር 13 ቀን 2009 ዓ.ም በአብደራፊ ከተማ ዙሪያ በህወሓት መከላከያ ሰራዊት ላይ ተመሳሳይ የደፈጣ ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን ባደረገው ሰፊ የማጥቃት እርምጃም 25 በመግደልና 17 በማቁሰል በቅጥረኛው የህወሓት ጦር ላይ ጠንካራ ክንዱን በማሳረፍ የበላይነትን ተጎናፅፎ የህወሓት ቅጥረኛ ወታደሮችን እንቅስቃሴ በመግታት መበታተን እንደቻለ ሪፖረተራችን አክሎ ገልጿል፡፡
ጀግናው የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት እየፈፀመ ያለውን ቆራጥ ተጋድሎ ጥቃቱ በሚፈፀምበት ቦታ ሁሉ ሙሉ በሙሉ የህዝብን ድጋፍ እያገኘ ሲሆን የቆመለትን አላማ ከግብ ለማድረስ ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ትንሳኤ እስኪሆን ድረስም ጀግኖች የአርበኞች ግንቦት 7 ነበልባል ሰራዊት ወደፊት በመግፋት በተግባር የኢትዮጵያ አለኝታነታቸውን እያስመሰከሩ ይገኛሉ፡፡

Tuesday, November 22, 2016

Ethiopia: Amharas in Benishangul face displacement

ESAT News (November 22, 2016)
Amharas who have resettled and called it home in Benishangul Gumuz region since 30 years ago during the former Ethiopian regime have said  they are facing harassment and threat of displacement from their land.
The Amharas, who settled in Benishangul in a resettlement program in the former government are being threatened by authorities to leave the region, according to a source who spoke on the phone with ESAT.
Hundreds of Amharas in Asosa have been displaced after authorities gave their land to developers, forcing them to migrate to towns and other areas.
Meanwhile, security forces have detained several youth in Benishangul Gumuz following the martial law declared in October, sources told ESAT.
An estimated 80,000 Amharas live in Benishangul Gumuz region in western Ethiopia.

Monday, November 21, 2016

ማዕበል ከፋሲል የኔአለም

የትኛውም ለህዝብ ነጻነት የሚታገል ድርጅት ከውስጥም ከውጪም ማዕበል ያጋጥመዋል። በማዕ በል ሳይመታ ለውጤት የበቃ ድርጅት በታሪክ ያለ አይመስለኝም፤ ማዕበል የአንድ ድርጅት ተፈጥሮአዊ ባህሪው ነው ማለትም ይቻላል። የትኛውም ድርጅት ማዕበል እንዳይነሳ ማድረግ አይችልም፣ ውስጣዊ ማእበል እንዳይነሳ ማድረግ ቢችል እንኳን ውጫዊ ማዕበሉን በፍጹም ማስቀረት አይችልም። ትልቁ ነገር ድርጅቱ ማእበሉን እንዴት በጥበብ ያልፈዋል የሚለውን ጥያቄ መመለሱ ላይ ነው። ማእበል ለአንድ ድርጅት አወንታዊ ወይም አሉታዊ ነገሮችን ይዞ ይመጣል። አንዳንድ ድርጅቶች የተነሳባቸውን ማእበል በጥበብ ማለፍ ያቅታቸውና ይጠፋሉ ( የማእበል አሉታዊ ጎኑ መሆኑ ነው)፣ ሌሎቹ ደግሞ ማእበሉን ማለፍ ብቻ ሳይሆን ከማእበሉ ትምህርት ወስደውበት ተጠናክረው ይወጣሉ ( የማእበል አወንታዊ ጎኑ ነው)።